እ ኛ ም ሰ ለ ም ን

ESKEMECHE No 100

ከአርባ አራቱ ገዳም

በቅለን

ለተጎዱት ልንቆም

ምለን፤

ሌሎችን እንደራሳችን

ልንወድ

የሰው ፍጡርን

ላናስወግድ፤

ሀሰትን ላናስተናግድ

እውነትን ተሸክመን

ልንራምድ፤

በቁርባን በጥምቀት

አድገን

ለነፍሳችን ማደር

ፈልገን፤

ዝም ማለት

ስላልቻልን

ዘንድሮማ

እኛም ሰለምን።

እስላሞች ወገናችን

ሲጠቁ

በመስጂዳቸው

ሲወቁ፤

የፍትኅ ያለህ ሲሉ

እኛም ለፍትኅ

እንቆማለን፤

መሪዬን ልምረጥ ሲሉ

ለመብታቸው

እንነሳለን፤

ሕግ ይከበርልን ሲሉ

በሕግ አምላክ

እንላለን፤

እኛስ ምን ቀረን?

የተጠቂን ጥቃት

ለማሰማት

ፍትኅን እውነትን

ለማግኘት፤

አብረናቸው ተሰለፍን

እኛም ሰለምን።

About አንዱዓለም ተፈራ

በዐማራው ላይ እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጥፋት ዘመቻ፤ ለዐማራው ያለኝን ተቆርቋሪነት ወደ ላይ አጡዞት፤ የምችለውን በሙሉ ለዚህ ለተዘመተበት ዐማራ ሕልውና ለማድረግ የቆምኩ ታጋይ።
This entry was posted in እስከመቼ - ESKEMECHE. Bookmark the permalink.

3 Responses to እ ኛ ም ሰ ለ ም ን

  1. ፒንግባክ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች | eske.meche

  2. ፒንግባክ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች – አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ | Derege Negash

  3. ፒንግባክ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች

አስተያየት ያስቀምጡ