ከአርባ አራቱ ገዳም
በቅለን
ለተጎዱት ልንቆም
ምለን፤
ሌሎችን እንደራሳችን
ልንወድ
የሰው ፍጡርን
ላናስወግድ፤
ሀሰትን ላናስተናግድ
እውነትን ተሸክመን
ልንራምድ፤
በቁርባን በጥምቀት
አድገን
ለነፍሳችን ማደር
ፈልገን፤
ዝም ማለት
ስላልቻልን
ዘንድሮማ
እኛም ሰለምን።
እስላሞች ወገናችን
ሲጠቁ
በመስጂዳቸው
ሲወቁ፤
የፍትኅ ያለህ ሲሉ
እኛም ለፍትኅ
እንቆማለን፤
መሪዬን ልምረጥ ሲሉ
ለመብታቸው
እንነሳለን፤
ሕግ ይከበርልን ሲሉ
በሕግ አምላክ
እንላለን፤
እኛስ ምን ቀረን?
የተጠቂን ጥቃት
ለማሰማት
ፍትኅን እውነትን
ለማግኘት፤
አብረናቸው ተሰለፍን
እኛም ሰለምን።
ፒንግባክ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች | eske.meche
ፒንግባክ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች – አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ | Derege Negash
ፒንግባክ፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች