በረራ፤ የ፲፭ኛው ከፍለ ዘመንና የ፲፮ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የነገሥታት ከተማ

Berara - በረራየጽሑፉ ጭምቅ ይዘት፤

በረራ፤ የ፲ ፭ኛው ከፍለ ዘመንና የ፲ ፮ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የነገሥታት ከተማ (ኢትዮጵያ)፤ በየረር ተራራና ወጨጫ ሸንተረሮች፤ በመካከለኛው ክፍለ ዘመን እና ከዚያ ቀደም የነበረ ሕዝብ ሰፈራ፤ የቅርብ ጊዜ የምርምር ጥናቶች ውጤት፤

ይህ ጽሑፍ፤ የበረራን እና በ፲ ፭ኛው ከፍለ ዘመን እና በ፲ ፮ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ የነበሩ የሰፈራ ቦታዎችን ታሪክኅ ዞሮ ይመረምርና፤ ታሪካዊ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ የሆነችውን በረራን፤ ቦታዋን ለይቶ፤ በደቡብ ሸዋ፤ በአሁኗ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ፤ አዲስ አበባ ከተማ አቅራቢያ፤ መሆኗን ለማመላከት የታሰበውን የመስክ ጥናት ውጤቶችን ይገልጣል። ታሪካዊ ምንጮች እና የሳተላይት የጥልቀት ዕይታዎች፣ የመልክዐ ምድር አቀማመጥ ሁኔታዎች እና ተጨባጭ የአካባቢ መሬት ጥናቶች ላይ በመንተራስ፤ ደራሲዎቹ ወደኋላ ወደ ቅድመ መካከለኛው ክፍለ ዘመን የሚደርሱ የሚመስሉ አዳዲስ ቦታዎችን በማሳወቅ፤ ረጅሙን እና የኢትዮጵያ የዚህ አካባቢ አስካሁን ያልታወቀ ታሪክ አሳይተውናል። ሆኖም ግን፤ በረራን በትክክል ቦታው ላይ ማስቀመጡ አዳጋች ሆኗል። እናም የመካከለኛው ዘመን በኢትዮጵያ የክርስቲያን “ከተሞች” ዕውቀታችን እንዲዳብርና እስካሁን በትክክል ያልተጠናውን ለሕዝቡና ለባህሉ እንቅስቃሴው ማዕከላዊ የሆነውን የዚህ አካባቢ የቅድመ መካከለኛው ዘመን ታሪክ እንዲገልጥልን፥ ተጨማሪ ጥናቶች ያስፈልጋሉ።

( ሙሉውን በፒዲኤፍ ለማንበብ ይሄን ይጫኑ –>  የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጥራዝ ፪ ሺህ ፩ – ፪ ቅጽ ፳፬, ገጽ ፪፻፱ እስከ ፪፻፵፱

About አንዱዓለም ተፈራ

በዐማራው ላይ እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጥፋት ዘመቻ፤ ለዐማራው ያለኝን ተቆርቋሪነት ወደ ላይ አጡዞት፤ የምችለውን በሙሉ ለዚህ ለተዘመተበት ዐማራ ሕልውና ለማድረግ የቆምኩ ታጋይ።
This entry was posted in እስከመቼ - ESKEMECHE. Bookmark the permalink.

አስተያየት ያስቀምጡ